YESLASE MAHBER FELLOWSHIP
ኅብረት — Fellowship
Our Spiritual Communion
“እንዲሁም እርስ በርሳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።” — ፩ኛ የዮሐንስ መልእክት ፩፥፯
የቅዱሳን ኅብረት፡- በክርስቶስ አንድ የመሆን ሚስጢር
ቤተክርስቲያን በሰው እጅ የተገነባ ድርጅት አይደለችም—እርሷ ከአብ፣ ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ ዘላለማዊ ኅብረት የተወለደች ሕያው አካል ናት። ዓለም ከመፈጠሩ በፊት አብ、 ወልድና መንፈስ ፍጹም በሆነ አንድነት、 ወሰን በሌለው ፍቅርና የጋራ ሕይወት ኅብረት ውስጥ ይኖሩ ነበር። ክርስቶስ የመጣው ከዚህ መለኮታዊ ሙላትና ፍሰት የተነሳ ነው—ኃጢአታችንን ሙሉ በሙሉ ይቅር ለማለት ብቻ ሳይሆን、 እርሱ ከአብ ጋር ለዘላለም ሲደሰትበት ወደነበረው ሕይወትና ኅብረት ሊያመጣን ነው (ዮሐንስ 17:21-23、 1 ዮሐንስ 1:3)። “ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ።” በማለት ያቀረበው ጸሎት መልስ ሳያገኝ አልቀረም። በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ፣ አስደናቂ ፍጻሜውን እናያለን፦ አንድ ልብ、 አንዲት ነፍስ、 አንድ ፍቅር ያላቸው ክርስቲያኖች በመንፈስ ቅዱስ ሲወለዱና ሲገለጡ እናያለን፡፡ እነዚህ የመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ክርስቲያኖች ሁሉንም ነገር በጋራ እስከሚያደርጉ ድረስ አንድነታቸውና ፍቅራቸው የጠበቀ ነበር፡፡ ይህም የሆነው ከግዴታ ሳይሆን、 ከተካፈሉት መለኮታዊ ሕይወት መፍሰስ የተነሳ ነው (የሐዋርያት ሥራ 2:44-47、 የሐዋርያት ሥራ 4:32)። ይህ ኅብረት ሃይማኖታዊ ፕሮግራም አልነበረም። ይህ ሥሉስ ቅዱስ በልጆቹ ውስጥ ሞልቶ ሲኖርና ሲንቀሳቀስ የሚያሳይ ነበር። ሐዋርያው ጳውሎስ ይህንን ምስጢር በጥልቅ አይቶ በድፍረት—ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካል ናት、 ክርስቶስም ራሷ ነው በማለት አወጀ (ኤፌ. 1:22-23)። እያንዳንዱ አማኝ በአባልነት ዝርዝሮች ወይም በአስተምህሮ ስምምነት ብቻ ሳይሆን በአንድ መንፈስ በአንድ ጌታ በአንድ ሕይወት የተገናኘ ነው (ኤፌ. 4:4-6)። እንደ ቤተክርስቲያን መኖር ማለት በዚህ የጋራ በሆነ ሕይወት መኖር ማለት ነው—እርሱ እንደወደደ መውደድ、 እርሱና አብ አንድ እንደሆኑ አንድ መሆን በምድር ላይ የክርስቶስ ሙላትና መገለጫ ከመሆን ያነሰ መሆን የለበትም። ይህ እውነተኛው የቤተክርስቲያን ሕይወት ነው—የምንገኝበት ስብሰባ ሳይሆን በእርሱ ውስጥ አብረን የምንኖረው ሕይወት ነው።
The church is not an organization built by human hands — she is a living organism, born out of the eternal fellowship of the Father, the Son, and the Holy Spirit. Before the foundation of the world, the Father, Son, and Spirit dwelt together in perfect oneness, in a fellowship of boundless love and shared life. It was out of this divine abundance that Christ came — not merely to forgive our sins, though He fully did — but to bring us into that very life and fellowship He has eternally enjoyed with the Father (John 17:21-23, 1 John 1:3). His prayer to the Father — “that they all may be one, as You, Father, are in Me, and I in You, that they also may be in Us” — was not left unanswered. In the book of Acts, we behold its glorious fulfillment: a community of believers with one heart, one soul, one love, holding all things in common, not out of obligation, but out of the overflow of a shared divine life (Acts 2:44-47, Acts 4:32). This was no religious program. This was the Triune God living and moving in human vessels. The Apostle Paul saw this mystery deeply and declared it boldly — the church is the Body of Christ, and Christ is her Head (Eph. 1:22-23). Every member is joined not by membership rolls or doctrinal agreement alone, but by one Spirit, one Lord, one life (Eph. 4:4-6). To live as the church is to live from this shared life — to love as He loved, to be one as He and the Father are one, to be nothing less than the fullness and expression of Christ on the earth. This is the true church life — not a meeting we attend, but a life we share together in Him.