እግዚአብሔር ይህንን ሁሉ ፍጥረት የፈጠረው የሚታየውንና የማይታየውን ሁሉ የሰራው ይህንን ውብ ፕላኔት ጨረቃን ጸሐይንና ከዋክብትን በመጨረሻም የሰውን ልጅ በራሱ መልክና አምሳል የፈጠረው ከምን ተነስቶ እንደሆነ ጠይቃችሁ ታውቃላሁ?? መቸም አንድ ነገር ሲሰራ ሲፈጠር መነሻ ምክንያት አለው፡፡ እንኳንስ ይህ ሁሉ ውስብስብ ንድፈ ፍጥረት ቀርቶ የሰው ልጅ እንኳ አንድ ነገር ሲሰራ በመጀመሪያ አስቦና አቅዶ ነው፡፡ ከተቀመጣችሁበት ወንበር ጀምሮ የምትጠቀሙባቸው ጥቃቅን እቃዎች ሁሉ ሳይቀሩ ለአንድ ዓላማ ታስበው የተሰሩ ናቸው፡፡ የምትነዱ መኪና የምትበሩበት አውሮፕላን በእጃችሁ የያዛችሁት ስልክ እና በቢሮአችሁ ያለው ኮምፒውተር ወዘተ ሰው ለተለያዩ ዓላማዎች አስቦና አቅዶ የፈጠራቸው ናቸው፡፡