But We እኛ ግን

እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፡፡


መቼም አይሁድ ምልክትን ይለምናሉ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ፥
እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ይህም ለአይሁድ ማሰናከያ ለአሕዛብም ሞኝነት ነው፥
ለተጠሩት ግን፥ አይሁድ ቢሆኑ የግሪክ ሰዎችም ቢሆኑ፥ የእግዚአብሔር ኃይልና የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው ክርስቶስ ነው።
” 1. ቆሮ 1፡22-24

በመምህር ጸጋ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ 

እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፡፡

 

“መቼም አይሁድ ምልክትን ይለምናሉ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ፥ እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ይህም ለአይሁድ ማሰናከያ ለአሕዛብም ሞኝነት ነው፥” 1 ቆሮ 1፤22-23

ቅዱስ ጳውሎስ በሥጋ ከአይሁድ ዘር እንደሆነ የታወቀ ቢሆንም በዚህ ስፍራ ግን ራሱን ከአይሁድ ህዝብ ውጭ አድርጎ መቼም አይሁድ ምልክትን ይለምናሉ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይሻሉ ካለ በኋላ እኛ ግን በማለት ራሱን ከሌላ ወገን ጋር ይቆጥራል፡፡ እርሱ ራሱ ከአይሁድ ሆኖ እንዴት ወደ ውጭ እያመለከተ ሁለተኛ ወገንን በሚጠቁም መልክ  አይሁድ ምልክትን ይለምናሉ ብሎ ይናገራል?? ለመሆኑ ራሱን አስገብቶ እኛ ግን ብሎ የጠቀሰው ወገንስ የቱ ነው? ኦ ይህ ቅዱስ ጥያቄ ነው መልሱ ደግሞ ቅድስተ ቅዱሳን፡፡ እርስዎም ከሚኖሩበት ካደጉበት የኔ ካሉት ምድራዊ ዘርና ባህል ከተላበሰ የሞተ ማህበረሰብ ወጥተው እነርሱ ብለው ይናገሩ ዘንድ ቅዱሱ ወንጌል የሚያለብስዎትን አዲሱን ሰው ለመልበስ ቃሉን በእምነት ይስሙ፡፡   

 

ቤተ ክርስቲያን ከምድር አህዛብና ነገሥታት ጋር አትቆጠርም፡፡ ቤተ ክርስቲያን ድንበርዋ የአገር ድንበር አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን በምድር ላይ ድንበር የሌላት ሰማያዊ ማሕበር ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን አካላዊ ድንበርዋ ዓለም ሁሉ ነው፡፡ በአሜሪካ ያለችን ቤተ ክርስቲያን የአሜሪካ ድንበር አይወስናትም  በኢትዮጵያ ያለችን ቤተ ክርስቲያን የኢትዮጵያ ድንበር አይወስናትም፡፡ ቤተ ክርስቲያን በዓለም ላይ ሁሉ ያለች አንዲት አካል ናት፡፡

እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን

ከዚህ በታች ያለውን የወንጌል ድምጽ እንዲሰሙ በታላቅ ፍቅር እንጋብዝዎታለን፡፡

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *