ስለዚህ እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችን በፍጹም ነፍሳችን በፍጹም ሐሳባችን ከወደድነው ከርሱ አልፈን የምንወደው ነገር የለንም፡፡ እርሱ የልባችን ጉዞ ፍጻሜ የጉዞአችን መጨረሻ የእርካታችን ጣሪያ የህይወታችን መድረሻ ነው፡፡ በዚህ ፍቅር የምትወዱት ከሆነ እግዚአብሔር መተላለፊያና መሸጋገሪያችሁ ሳይሆን መድረሻችሁ ይሆናል፡፡ እርሱን የምንፈልገው በርሱ በኩል አንድ ነገር ለማግኘት ሳይሆን እርሱን ለማግኘት ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊት እንዳለው “ፊትህን እሻለሁ ልቤ አንተን አለ” እንለዋለን፡፡
እግዚአብሔር ልባችንን ወደርሱ ያቅና አሜን፡፡