Yeslase

የእግዚአብሔር ፍቅር ክፍል ሶስት

የእግዚአብሔር ፍቅር ክፍል ሶስት እግዚአብሔርም፦ ብርሃን ይሁን አለ፤ ብርሃንም ሆነ። ዘፍ.1:3 ብርሃን የህይወት ምንጭ ነው፡፡ ብርሃን ከሌለ ህይወት የለም፡፡ ስለዚህ ህይወት ያላቸውን ፍጥረታት ለማምጣት ብርሃን ይሁን በማለት ጀመረ፡፡ ከዚያም በውሀና በጭለማ ተወርሳ መልክ አልባና ባዶ የነበረችውን ምድር ያስውባት ጀመር፡፡ ከጠፈር በላይ ያለውን እና ከጠፈር በታች ያሉትን ውሆች በመለየት ጠፈሩን አደረገ፡፡ ከጠፈር በታች ያለውን ውሀ ወደ …

የእግዚአብሔር ፍቅር ክፍል ሶስት Read More »

ማንም የማይወስድብን ዕድል

ማንም የማይወስድብን ዕድል “ኢየሱስም መልሶ፦ ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥42 የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት። ሉቃ.10:41-42.” ብዙ ጊዜ ዘመናችንን ሁሉ ስናሳድድ የምንኖረው የሚጠፋውን ነገር ዛሬ አግኝተን ነገ የምናጣውን ነገር ነው። በተለይ የሰው ልጆች በእጅጉ ሲፈልጉት ቀንና ሌሊት ሲመኙትና ሲፈልጉት የሚኖሩት ዓለም አቀፍ ምኞት በመጽሐፍ ቅዱስ …

ማንም የማይወስድብን ዕድል Read More »

የሳምራዊትዋ ሴት ማስታወሻ

የሳምራዊትዋ ሴት ማስታወሻ ሕይወቴና ታሪኬ ከሰው ጋረ አያስኬደኝምሕይወቴ ውበት የለውምየሰዎች መጠቋቆሚያ ሆኜአለሁትኩር ብየ እንኳ ሰዎችን መመልከት አልችልምበቀትር ሁልጊዜ ምንጩ ባዶ ነበር።ዛሬ ግን አንድ ሰው አገኘሁአለባበሱ የአይሁድ ነውበዚህ ስፍራ ምን ያደርጋል?ኢየሱስ ክርስቶስ ውሀ አጠጪኝ ብሎ ሲጠይቀኝ።እንዴት ውሀ ይለምነኛል?እንኳንስ ውሀ ሊለምነኝ አይሁዳዊ አናግሮኝ አያውቅም።ንዴቴን በሚገልጽ ንግግር መቸም እናንተ አንድ ነገር ካልተቸገራችሁ አታናግሩንምብየ አሰብኩና አንተ የይሁዳ ሰው ስትሆን …

የሳምራዊትዋ ሴት ማስታወሻ Read More »

የእግዚአብሔር ፍቅር ክፍል ሁለት

ባለፈው መልእክታችን ሰው የሰራቸውን ነገሮች ሁሉ የሰራው ውስን የሆነውን ማንነቱን ይሞሉልኛል ብሎ እንደሆነ አይተን እግዚአብሔር ግን ሙሉና ፍጹም አምላክ ሆኖ ሳለ ይህንን ሁሉ ለምን ፈጠረ? የሚል ጥያቄ አንስተን ነበር፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔር ፍጹም አምላክ እንደሆነና ጉድለቱን ለመሙላት ምንም ነገር መፍጠር እንደማያስፈልገው ከተስማማን በመልኩ የፈጠረንን እኛን ጨምሮ ይህንን ሁሉ ፍጥረት የፈጠረበት ምክን ያት ከቃሉ እንመልከት፤፡

የእግዚአብሔር ፍቅር ክፍል አንድ

እግዚአብሔር ይህንን ሁሉ ፍጥረት የፈጠረው የሚታየውንና የማይታየውን ሁሉ የሰራው ይህንን ውብ ፕላኔት ጨረቃን ጸሐይንና ከዋክብትን በመጨረሻም የሰውን ልጅ በራሱ መልክና አምሳል የፈጠረው ከምን ተነስቶ እንደሆነ ጠይቃችሁ ታውቃላሁ?? መቸም አንድ ነገር ሲሰራ ሲፈጠር መነሻ ምክንያት አለው፡፡ እንኳንስ ይህ ሁሉ ውስብስብ ንድፈ ፍጥረት ቀርቶ የሰው ልጅ እንኳ አንድ ነገር ሲሰራ በመጀመሪያ አስቦና አቅዶ ነው፡፡ ከተቀመጣችሁበት ወንበር ጀምሮ የምትጠቀሙባቸው ጥቃቅን እቃዎች ሁሉ ሳይቀሩ ለአንድ ዓላማ ታስበው የተሰሩ ናቸው፡፡ የምትነዱ መኪና የምትበሩበት አውሮፕላን በእጃችሁ የያዛችሁት ስልክ እና በቢሮአችሁ ያለው ኮምፒውተር ወዘተ ሰው ለተለያዩ ዓላማዎች አስቦና አቅዶ የፈጠራቸው ናቸው፡፡